ወንጌል መስበክ ምን ማለት ነው?

ወንጌል መስበክ ማለት ክርስቶስ ኅጢአተኞችን ለማዳን ያደረገውን መልካም ዜና መናገር ነው። ይህንንም ለማድረግ እነዚህን እውነቶች የግድ መናገር ይኖርብናል፦

1. እግዚአብሔር ቅዱስ ነው (1ኛ ዮሐንስ 1፥5)። እርሱ የሚታይውም የማይታየውም ዓለም ፈጣሪ ነው።

2. ሰው ሁሉ ኅጢአተኛ ነው፤ ከዚህ የተነሣ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ የጽድቅ ፍርድ ይገባዋል (ሮሜ 3፥10-19፤ ማርቆስ 9፥48፤ ራዕይ 14፥11 )።

3. ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ፣ በዚህ ምድር ያለ ኅጢአት ተመላለሰ፤ በእርሱ ለሚያምኑ፣ በእነርሱ ፈንታ የእግዚአብሔርን ፍርድ በመስቀል ላይ ተቀበለ፤ የዘላለም ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ከሙታን ተነሣ (ዮሐንስ 1፥1፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥5፤ ዕብራውያን 7፥26፤ ሮሜ 3፥21-26፤ 2ኛ ቆሮንጦስ 5፥21፤ 1ኛ ቆሮንጦስ 15፥20-22)።

4.ከዘላለም ቅጣት ለማምለጥ እና ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር ብቸኛው መንገድ ንስሓ መግባት እና በክርስቶስ አዳኝነት ማመን ነው (ማርቆስ 1፥15፤ የሐዋሪያት ሥራ 20፥21)።

ወንጌል መስበክ ማለት እነዚህን ወሳኝ ነገሮች ማሳወቅ ነው።